
እውነት እላችኋለሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት እንደ ሕፃን የማቀበሉት ሁሉ ከቶ አይገባባትም አለ፡፡ ሉቃ 18፡17
እግዚአብሔር በጣም ቀላል፣ ያለለውን ጩኸት የሕፃናት ጥያቄ የሚመስለውን ፀሎት ይሰማል፡፡ እኔ አራት ልጆችን አድርሻለሁ፣ ዘጠኝ የልጅ ልጆች አሉኝ፡፡ ካለኝ ልምድ ልጆች ውስብሰብ አይደሉም፡፡ ልጆች የፈለጉትን ጠይቆ ለማወቅ፣ ስፈራ ሮጦ ወደ ትክሻ ሥር ለመግባት፣ ፍቅራቸውን የሚገልፁበት አሳሳም፣ አንዳንድ ጊዜ ግልፅ ያልሆነ የውስጣቸውን ስሜት የሚገልፁበት መሳሞች፡፡ ልጆች ወላጆቻቸውን ጥያቄ ሲጠይቁ ሙሉ በሙሉ መልስ እንደሚያገኙ በማመን ነው፡፡ ልክ እንደዛው እኛም እግዚአብሔርን ስናናግረው በዚሁ መንፈስ ሆነን መሆን አለብን፡፡ ልጆች ግልፆችና የልባቸውን ሃሣብ ለመሰወር ውስብስቦች ስላልሆኑ ከእነርሱ ጋር ኅብረጽ ማድረግ ቀላልና የሚያስደስት ይሆናል፡፡
እግዚአብሔርም የሚፈልገው ከእኛ ጋር ሲነጋር ልክ እንደ ሕፃናት እንድንሆን ይፈልጋል፡፡ እኛም እግዚአብሔርን ስንቀርብ እንደ ሕፃናት ቀለል ባለ መንገድ ከእርሱም ለመስማት በጣም በጉጉት እርሱ የሚለንን መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ ልጆች በተፈጥሮአቸው ሙሉ በሙሉ ወላጆቻቸውን ለመታመን ያጋደሉ እንደሆኑ ሁሉ እኛም ለእግዚአብሔር ድምፅ የዋ ንፁህና ያለፍርሃት ሆነን የእርሱን ድምፅ መስማት አለብን፡፡ ስንፀልይ በቀላሉ የሕፃናት እምነት በሚመስል በእግዚአብሔር ተዓምራዊ የሥራ ኃይል ነገሮች ተለውጦ እናገኛለን፡፡
ዛሬ የእግዚአብሔር ቃል ለአንተ፡- ዛሬ ወደ እግዚአብሔር ስትፀልይ ‹አባ› ብለህ በመጥራ ሙሉ በሙሉ በእርሱ ታመን፡፡