ዛሬ በፈቃዱ ራሱን ለእግዚአብሔር የሚቀድስ ማን ነው; 1 ዜና 29 5
ክርስቲያኖች ሕይወታቸውን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር አሳልፎ በመስጠት መኖር ሲጀምሩ ለጠላት አደገኞች ይሆኑበታል፡፡ እንደዚህ ዓይነት መስጠት የሚመጣው እራሳችንንና ያለንን ሁሉ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር በማቅረብ የሚመጣ ነው፡፡ ለእራሳችን የምናስቀረው ወይም ወደኋላ የምናደርገው ነገር የለም፡፡ እራሳችን ለእርሱ አሳልፈን ስንሰጥ በሕይወታችን እግዚአብሔር ስለእያንዳንዱ ጉዳይና ምርጫችን እንዲናገረንና አብሮን እንዲሆን መጋበዛችን ነው፡፡
ለእግዚአብሔር መለየታችንና ለእርሱ ጥቅም መዋላችን እርግጠኛ ከሆነ እራሳችን ልንጠይቅ የሚገባን ነገር ምናባት ለእግዚአብሔር ያላስረከብነውና ለእራሳችን የያዝነው ካለ ነው፡፡ ምን ያህል ትንሽ ይሁን የተደበቀ ሚስጥር ቦታዎች በልባችን አሉን; እንዲህና እንደዚያ የምላቸው ነገሮች ምንድናቸው እሺ እግዚአብሔር ሆይ፣ ሁሉን ነገር ወስደው ነገር ግን ያንን ወይም ኦ ይሄንማ አይሆንም እግዚአብሔር ሆይ ለዚህማ አልተዘጋጀውም! ወይም እግዚአብሔር ሆይ ያንን ግንኙነት እንኳ አትንካ ጌታ ሆይ ያንንማ ከማድረግ ዝም እንድል አትጠይቀኝ፡፡ የምንል ከሆነ ሙሉ መስጠት አይደለም፡፡ ጌታ ሆይ መጽሐፍ ቅዱስን በየቀኑ አነባለሁ ጥቅሶችን አሰላስላለሁ ቃልህን በልቤ ውስጥ እሰውራለሁ እንዲሁም በየቀኑ አነባለሁ ጥቅሶችን አሰላስላለሁ፡፡ ቃልህን በልቤ ውስጥ እሰውራለሁ እንዲሁም በየቀኑ ለብዙ ሰዓት እፀልያለሁ፡፡ ነገር ግን ይችን የእኔ የውስጤ ምርጫ (ሱሴን) እንዲተው አትጠይቀኝ! ›› አይደለም ሙሉ በሙሉ መስጠት ማለት በሙሉ እራስን ከልብ መስጠት ነው፡፡ ጌታ ሆይ እራሴን ሙሉ በሙሉ ለአንተ እሰጣለሁ በል፡፡ ጌታ ሆይ የፈለከውን ንገረኝ ደግሞ ተናገረኝ፡፡
እንዲህ ስል ግን እግዚአብሔር ለእኛ ደስታ የሆነውን ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ከእኛ እንደሚወስድ ማሰብ እንዳለብን ላሳሰብ እፈልጋለሁ፡፡ ምክንያቱም እርሱ ያንን አያደርግም፡፡ ነገር ግን ሁሉም ነገር በእርሱ ግልጽና የታወቀ መሆን አለበት፡፡ እርሱ በእርግጥ የምጠቅመንን ሊመርጥልን ይገባል፡፡ የእኛ ድርሻ ሙሉ በሙሉ በእርሱ መታመን ነው፡፡
ዛሬ የእግዚአብሔር ቃል ለአንተ፡- ለእግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ ታገኝለት ከእርሱ የምትሰውር ምንም ነገር አይኑርህ፡፡