የልመና እና የትጉ ጸሎት

አትለምኑምና ለእናንተ አይሀንም። (ያዕቆብ 4፤2)

እግዚአብሐር ያለ ምንም ትግል የምንፈልገቸውን ነገሮች ይኖሩን ዘንድ ቀለል ያለ መንገድ አዘጋጅቶልናል፡፡እነዚህን ነገሮች ለማግኘት እየታገልን ነው። የዛሬ ጥቅስ ምንም ስለማትለምኑ ምን አትቀበሉም የሚል መልዕከት ነው። ስለ አንድ ጉዳይ ከልተጸለየ የጸሎት መልስ ሊሆን አይችልም፡፡ስለዚህ የሚያስፈልጋንን ለማግኘት መጸለይና መጠየቅ ይኖርብናል ።የልመና ጸሎት ስናቀርብ የምንፀልየው ጸሎት የልመና ጸሎት ይባላል፡፡ ስለዚህ እንዲህ ዓይነቱ ፀሎት አስፈላጊ ነው፡፡ እግዚአብሐር ሰው ካልጸለየና የሚያስፈልጋውን እንደ ፈቃዱ ካልጠየቀ የሚገባውን ነገር አየገኝም፡፡ ምክንያቱም ሰው ከእግዚአብሐር ጋር ግንኙነት ከሚያደርግባቸው መንገዶች ዋናው በጸሎት አማካኝነት ነው ። ጸሎት በተፈጥሯዊው ዓለም ውስጥ በመንፈሳዊው ዓለም ነገሮችን ለማከናወን ይሰራል ። ጸሎት የሰማይን ኃይል ወደ ምድር ያመጣል፡፡

ጸሎታችን ቶሎ ካልተመለሰ ቆም ብለን ልንጠይቅ እንችላለን ይህ የእግዚአብሔር ፍቃድ አይደለም ወይም ነው እግዚአብሔር ሊመልስልን ጠብቅ ሊላን ይችላል፡ ምክንያቱም በእርሱ እምነታችንን እያዳበርን እና መንፈሳዊ አቅማችንን እንድንገነባ ጽናትንና ትዕግሥትን መመር የስፈልጋል፡፡

እግዚአብሐርን መለመንና ልመናችንን ለእርሱ ማሳወቅ ይኖርብናል እንጂ እኛ በራሳችን ጥረት ነገሮች እንዲከነወኑ ለማድረግ መሞከር ዉጤት የለዉም ። ከእኛ የሚጠበቀው ነገር ቢኖር በእርሱ መታመንና በጥበብ እንዴትና መቼ ጸሎት እንደሚመልስ በትዕግስት ለእግዚአብሔር ስራ ልባችን መክፈት, ነገር ግን የሚያስፈልጉንን ነገሮች በራሳችን ጥረት ለማግኘት መሞከራችን ከንቱ ከመሆኑም በላይ የእግዚአብሔርን ስራ ያደናቅፋል ።ስለዚህ የምጠበቅብንን በማድረግ እና በእምነት በጸሎት በፊቱ መቆየት ይጠበቅብናል።እንዲህ ስናደርግ እግዚአብሔር በእኛ ሕይወት አስደነቂ ስራን ይሠራል ።


የእግዚአብሔ ቃል ለአንተ ዛሬ -እግዚአብሔር ልትገምት ከምትለው በላይ የበለጠ ሊያደርግልህ ይፈልጋል፤ ስለዚህ በድፍረት በጸሎት እርሱን መለመን አለብህ፡፡

Facebook icon Twitter icon Instagram icon Pinterest icon Google+ icon YouTube icon LinkedIn icon Contact icon